84 İNŞİKAK
-
84:1
ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
-
84:2
ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤
-
84:3
ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤
-
84:4
በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤
-
84:5
ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡
-
84:6
አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡
-
84:7
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤
-
84:8
በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡
-
84:9
ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡
-
84:10
መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤
-
84:11
(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡
-
84:12
የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡
-
84:13
እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡
-
84:14
እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡
-
84:15
አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡
-
84:16
አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡
-
84:17
በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤
-
84:18
በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡
-
84:19
ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡
-
84:20
የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?
-
84:21
በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)
-
84:22
በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡
-
84:23
አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡
-
84:24
በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡
-
84:25
ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡

