99 ZİLZAL
-
99:1
ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤
-
99:2
ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤
-
99:3
ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤
-
99:4
በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡
-
99:5
ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡
-
99:6
በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡
-
99:7
የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡
-
99:8
የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡
Paylaş

Tweet'le
